[smartslider3 slider="3"]

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. ማኅበረ ቅዱሳን ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናትና ምርምር ማእከል›› በመክፈት ቅዱሳት መጻሕፍትን ማስተዋወቅ እና ከሚደርስባቸው ልዩ ልዩ ጉዳዮች አደጋዎች ተጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላላፉ ማድረግ ያቋቋመው የአገልግሎት ክፍል ለዛሬው የጥናትና ምርምር ማእከል መመሥረት ምክንያት ነው። ይህ ክፍል በተሻለ አደረጃጀትና የሰው ኃይል ተጠናክሮ ከኅዳር ወር ፳፻፩ ዓ.ም. ጀምሮ ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል›› በሚል ስያሜ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ማኅበረ ቅዱሳን በአዲስ ምዕራፍ!

ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ የመተዳደሪያ ደንቡ ጸድቆ ከተሰጠው ጀምሮ አገልግሎቱን የተሻለ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ ማኅበሩ ርእይዩን ከግብ ለማድረስ በሀገር ውስጥና በልዩ ልዩ የውጭ ሀገራት የአገልግሎት መዋቅርን ዘርግቶ ተተኪ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በማፍራት፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ወጣቶች በሥነ ምግባር እንዲታነጹ በማድረግ ሀገርና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በዕውቀታቸው፣ በገንዘባቸውና በሙያቸው የሚያገለግሉ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እያፈራ ይገኛል። ይህንን መጠነ ሰፊ አገልግሎት ለማሳለጥና በሚፈለገው ልክ አገልግሎቱን ለማስሄድ ሁለተኛ ዙር ጽሕፈት ቤት መገንባት ግድ ሆኖበታል። ማኅበሩ እየተጠቀመበት ያለው ሕንጻ ዕለት ዕለት እያደገ ከመጣው የማኅበሩ የአገልግሎት መስፋት አንጻር ሲነጻጸር ተመጣጣኝ ባለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት የሁለተኛ ዙር ጽሕፈት ቤት ግንባታ በይፋ ጀምሯል።

መልካም አስተዳደር ለሀገር ሰላም

የመልካምነት ሁሉ መገኛ የሆነችው፣ ሰብሳቢያችን፣ አስተማሪያችን፣ ቅድስት ስፍራ፣ የእውነተኛ ሕይወት መገኛ፣ የአምላክ ቤት መቅደሳችን በዚህ ጊዜ ተከፍታለች፡፡ ልጆቿን በስደት፣ በሞትና በኃጢአት በማጣቷ ሰላምን ማግኘት አልቻለችም፡፡ ይህን ሰላም ማግኘት የምትችለውም ልጆችዋን በቤቷ ስትሰበስብና በመልካም አስተዳደር ማኖር ስትችል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ዛሬም ዘወትርም በጥላዋ ሥር እንድንከለል የምትጠራንም ለዚህ ነው፡፡ በቤቷ፣ በቅድስናው ስፍራ እንድንኖርም ታስተምረናለች፤ ትመከረናለች፡፡

ይህን የአምላካችንም የሰላም ጥሪ መስማትና ወደ ቤቱ መመለስ ደግሞ ከእኛ ይጠበቃል፡፡ የሰላም ባለቤት የሆነው ጌታችን ካለንበት ሥቃይ አውጥቶ፣ ችግራችንን ፈትቶና ከመከራ አውጥቶ በመልካሙ፣ በጽድቁ ጎዳና ይመራናል፤ እውነተኛ መንገድ እርሱ ነውና፤ ‹‹እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ›› እንዲል፡፡ (ዮሐ.፲፬፥፮) ሕዝብ ሰላም ከሆነ ሀገር ሰላም ይሆናል፤ ሀገር ሰላም የምትሆነው ደግሞ የሁሉ ፈጣሪ አምላካችን እግዚአብሔር ሲከበር፣ ሲፈራ፣ ሲመለክና ቤቱ በቅድስና ሲጠብቅ ነው፡፡