• እንኳን በደኅና መጡ !

የትንሣኤ ትሩፋቶች

ከመምህር ተፈሪ መንገሻ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የክርስትና እምነት መሠረትና የሰው ልጅ ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገረበት የድል አዋጅ ነው። ከትንሣኤ እስከ ዕርገት ያሉት አርባ ቀናት እንዲሁም እስከ በዓለ ኀምሳ ያሉት ዐሥር ቀናት ቤተክርስቲያን የተመሠረተችባቸውና ሰማያዊው ሥርዓት ለሐዋርያት የተሰጠባቸው ልዩ ወቅቶች ናቸው። ፅንስ በማሕፀን እስከ አርባ ቀን ድረስ ተሥዕሎ መልክእ እንደሚሰጠው ክርስቶስም በሐዋርያት ልብ ቤተክርስቲያንን እየሣለላቸው […]

ቅዳሜ

ቅዳሜ ከመምህር አዲሱ በዛብህ የትንሣኤ ሳምንት ቅዳሜ ቅዱሳት_አንስት_ይባላል። በወንጌል ተጽፎ እንደምናነበው ፍቅሩን በማሰብ ጨለማውን ሳይፈሩ ወደ መቃብር ስለመጡት መግደላዊት ማርያም እና ማርያም ባውፍልያ በስፋት ቤተክርስቲያን እንድናስብ ስለምታስተምረን ቅዱሳት አንስት ተብሏል። ወንጌሉ ስለዚህ ዕለት እንዲህ ብሎ ይገልጻል: – “ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።እየሮጠችም ወደ ስምዖን […]

አዳም

ከመምህር ተስፋ ሚካኤል ታደለ በቤተክርስቲያን ትውፊት ሐሙስ “የአዳም ሐሙስ” ተብላ የምትታወቀው አዳም የተፈጠረባት ዕለት ስለሆነች ሳይሆን፣ ከገነት ተባርሮ መከራ ሲቀበል እግዚአብሔር የመመለስ ተስፋውን የሰጠበት ዕለት በመሆኗ ነው። (መጽሐፈ አክሲማሮስ ፣ ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ሳዊሮስ ስለ ድኅነተ አዳም በተናገረበት) አዳም በስድስተኛው ቀን (ዓርብ) ተፈጥሮ በዕለተ ዓርብ ቢበድልም፣ እግዚአብሔር ግን በመከራው ውስጥ ተስፋ እንዲሆነው “በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን