• እንኳን በደኅና መጡ !

ቃና ዘገሊላ

በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ!

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! በመ/ር ቢትወደድ ወርቁ የልደትና የጥምቀት ዘመን በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋኒ፣ በግእዝ ዘመነ አስተርእዮ፣ በአማርኛ የመገለጥ ዘመን ይባላል። ጥምቀት የሚለው ቃል “አጥመቀ” ከሚለው የግእዝ ቃል/ግሥ የተገኘ ሲሆን በቀጥታ ሲተረጎም በውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት፣ መጠመቅ ማለት ነው። በምሥጢራዊ ትርጉሙ ግን ጥምቀት ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንዱ ሲሆን ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ተወልደን የሥላሴን […]

“ኦ ዝ መንክር ልደተ አምላክ እማርያም እምቅድስት ድንግል አግመረቶ ለቃል ኢቀደሞ ዘርዕ ለልደቱ” (ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ)

በመ/ር ታዴዎስ መንግስቴ የእግዚአብሔር ሰው የመሆን ምሥጢር በሰው አእምሮ አይደለም በመላእክት ኅሊናም ለመረዳት የማይቻል ረቂቅ፣ የማይመረመር ምሥጢር፣ የማይደረስበት ሩቅ፣ ዝም ብለው የሚያደንቁት ግሩም ነው። ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ድንግል ማርያምን ባመሰገነበት ውዳሴው “ኦ ዝ መንክር ልደተ አምላክ እማርያም እምቅድስት ድንግል አግመረቶ ለቃል ኢቀደሞ ዘርዕ ለልደቱ፤ ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይደንቅ፣ ቃልን ወሰነችው […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን