“በሕይወት መኖር የሚፈልግ ከክፉ ይሽሽ መልካሙንም ያድርግ”
በዚህ ወቅቱ ዓለም በከባድ እና አስቸጋሪ ፈተና ውስጥ ነው፡፡ ይህን ቸነፈር በሰው ጥንቃቄ ብቻ መቋቋም የሚቻል አይደለም፡፡ ሆኖም በግዴለሽነት እንዳንጓዝ ይልቁንም አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባን ቅዱሳት መጻሕፍት ይመክሩናል፡፡ በሃይማኖት ጸንተው በምግባር ቀንተው፣ ጥንቃቄም አድርገው የኖሩ አባቶቻችን በነፍሳቸውም፣ በሥጋቸውም ድነዋል፡፡ እኛም አባቶቻችንን አብነት አድርገን በነፍስም በሥጋም እንድንድን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡