የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር በአቀባበል መርሐ ግብር ተጀመረ

ማኅበረ ቅዱሳን ፲፪ኛው የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር ላይ ለመሳተፍ ለሚመጡ የማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ተወካዮች አቀባበል እያደረገ ይገኛል፡፡

የአቀባበል ሥርዓቱም በሕጽበተ እግር የተጀመረ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ፫ኛ ወለል ላይ በመከናወን ላይ ነው፡፡ በዚህ ሴሚናር ላይ ፫፻ የማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ተወካየች የሚሳተፉ ሲሆን ጉባኤው ለሁለት ቀናት ከሐምሌ ፳፫-፳፬ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም እንደሚካሄድ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ ገልጿል፡፡

ከአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ በኋላም ጉባኤው በእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክትይቀጥላል፡፡

ሂደቱን እየተከታተልን የምናቀርብ ይሆናል፡፡

 

0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *