የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው በመሔድ ላይ ይገኛሉ

የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚችለውን አደጋ ለመቀነስና ለመታደግ ወደየቤተሰቦቻቸው እንዲሔዱ በወሰነው መሠረት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን በመሸኘት ላይ ይገኛሉ፡፡

የትራንስፖርት አቅርቦቱ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር የተቀናጀ ሥራ በመሥራትና በማመቻቸት ለተማሪዎቹ እንደሚቀርብ የተገለጸ ሲሆን ላልተወሰነ ጊዜ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሚቆዩበት ወቅት ትምህርታቸውን እያጠኑ እንዲቆዩ ተነግሯቸዋል፡፡

የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችም ስለ ቫይረሱ ስርጭት በቂ ግንዛቤ ይዘው ወደየቤተሰቦቻቸው በመሔድ ቤተሰብን የማሳወቅና የመንከባከብ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም ወቅቱ የሱባኤ ወቅት በመሆኑ በጾም በጸሎት እየበረቱ፣ ራሳቸውንም እየጠበቁ ሌሎችን ስለ ቫይረሱና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች በማስተማር፣ በመርዳትና በመንከባከብ ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡

0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *