New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና የ«ተሐድሶዎች» ቅሰጣ

                                    በእደማርያም ንርአዩ

ምድራችን እስከ ዕለተ ምጽአት ከመልካም ስንዴው ጋር እንክርዳዱን ማብቀሏ፤ ከየዋሁ በግ ጋር ተኩላውን ማሰለፏ፤ ከንጹሐን ሐዋርያት መካከል ይሁዳን ማስገኘቷ አይቀርም፡፡ እንክርዳዱ እንዳይነቀል ከስንዴው ጋር አብሮ በቅሎ፣ ተኩላው እንዳይጋለጥ በግ ይመስል ዘንድ ለምድ ለብሶ ከስንዴው ጋር ልዘናፈል፣ ከበጉም ጋር ልመሳሰል ብለው ያልሆኑትን ለመሆን እየታገሉ ለዓላማቸው መስለው የሚሠሩ ተቆርቋሪም ሆነው የሚቀርቡ በማባበል ቃል የሚጎዱ ከፍጥረት ጅማሬ እስከ ዘመን ፍጻሜ፤ ከመላእክት ከተማ እስከ ደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን እስከሚገለጥበት ቦታ ከገነት እስከ ዛሬዋ መቅደስ ስተው እያሳቱ ክደው እያስካዱ ከዚህ ዘመን ደርሰዋል፡፡