New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

«ለራሱ ገንዘብ የሚያመቻች በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ባለጠጋ ያልሆነ ሰው እንዲህ ነው»

ሦስተኛ እሑድ

 

 /ሉቃ. 12.21/

ጌታችን በይሁዳ አካባቢዎች እየተዘዋወረ ሲያስተምር ከህዝቡ አንድ ሰው ቀርቦ፡- «መምህር ሆይ ርስቱን ከእኔ ጋር እንዲካፈል ለወንድሜ ንገረው» አለው፡፡ ጌታችን ግን ወደዚህ ምድር የመጣው፣ ለመለኮታዊ /ሰማያዊ/ ዓላማና የሰውን ልጆች ለማዳን እንጂ በሰዎች ምድራዊ ኑሮ ገብቶ ሃብትን ለማከፋፈል ባለመሆኑ፣ ዳግመኛም እርሱ የመጣው ራስን ለሰው መስጠትን፣ ፍቅርንና አንድ መሆንን የምትሰብከውን ወንጌልን ለመስራት በመሆኑ «አንተ ሰው ፈራጅና አካፋይ እንዲሆን በላያችሁ ማን ሾመኝ?» በማለት ይህንን ሊያደርግ እንደማይወድ ከተናገረ በኋላ አጋጣሚውን በመጠቀም አብረውት ለነበሩት እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፤ «የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፤ ከመጎመጀትም ሁሉ ተጠበቁ»፡፡