New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

«ተዋሕዶ ለአንድሮይድ» የተሰኘ የስልክ ላይ አገልግሎት ተጀመረ

 የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም.

በዝግጅት ክፍሉ ሪፖርተር

 google play news 4

google play news 2በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል ሚድያና ቴክኖሎጂ ክፍል «ተዋሕዶ ለአንድሮይድ» የተሰኘ የቴሌፎን አገልግሎት መስመር ዘረጋ፡፡ አገልግሎቱ በተለይ የእጅ ስልካቸው ወይም የኪስ ኮምፒዩተራቸው /ታብሌት/ አንድሮይድ በተሰኘው ግብረ ቴክኖሎጂ /ኦፕሬቲንግ ሲስተም/ አማካይነት የሚሠራ ምእመናን በያሉበት ኾነው በቀላሉ ልዩ ልዩ ትምህርቶችን፣ መዝሙራትን፣ የዕለትና የበዓላት ንባባትን /ግጻዌን/፣ በድምጽና በምስል የቀረቡ መንፈሳዊ ትረካዎችንና ጭውውቶችን፣ ልዩ ልዩ የጸሎት መጻሕፍትን እንዲሁም በሰሜን አሜሪካ በልዩ ልዩ ግዛቶች ስለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያደርስ ኾኖ የተዘጋጀ ነው፡፡