ዶክተር ብርሃኑ ተሾመ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ!
ዶክተር ብርሃኑ ተሾመ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ፵፩ ዓመቱ ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞተ ተለይተዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም በደብረ ምጥማቃት ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል የካቲት ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፈጽሟል፡፡
ዶክተር ብርሃኑ ተሾመ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ፵፩ ዓመቱ ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞተ ተለይተዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም በደብረ ምጥማቃት ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል የካቲት ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፈጽሟል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኢሬኔጅ የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ።
የ፳፻፲፫ መስቀል ደመራ በዓል የኮሮና በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ አምስት ሺህ ተሳታፊዎች ብቻ በተገኙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ተከብሯል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን የፀጥታ ሥጋት እንዳለባቸው ለዝግጅት ክፍላችን ተናገሩ፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የሀዋሳ ማእከል ሕግና ዕቅበተ እምነት አገልግሎት ዋና ክፍል ተጠሪ የነበሩት አቶ አስማማው ታመነ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በደረሰባቸው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው እንዳለፈ የሀዋሳ ማእከል አስታወቀ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጅማ ሀገረ ስብከት የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የተላለፍወን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሽፋን በማድረግ አግባብ ያልሆነ እስርና እንግልት በምእመናንና በአባቶች ላይ እየተፈጸመ መሆኑን በማኅበረ ቅዱሳን የጅማ ማእከል አስታወቀ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሜታ ሮቢ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘውን የሙጤ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ቅርስ ዘርፈው እጅ ከፍንጅ የተያዙ አራት ግለሰቦች በፍርድ ቤት ትእዛዝ ከእስር መፈታታቸውን የወዳ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስኪያጅ መሪጌታ ክፍሌ ቱቦ አስታወቁ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በኮሌራ ወረርሽኝ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው የዳሰነች ሕዝበ ክርስቲያን የእርዳታ ድጋፍ ተደረገ፡፡
ዘጠነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ በመጭው እሑድ ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ/ም ሊካሄድ እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ መምህር ዕንቈ ባሕርይ ተከሥተ አስታወቁ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም የመጻሕፍተ ሐዲሳት እና ሊቃውንት ጉባኤ ቤት 18 የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት ኅዳር 21 ቀን 2012 ዓ.ም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመረቁ፡፡
ፖስታ ሳጥን ቁጥር ፡ 80078
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
ድረገጽ: www.eotcmk.org
ጌታ ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰጥቶታል ያንን መስራት የእሱ ፈንታ ነዉ። ቢቻለዉ እሱን ማገድ የዲያብሎስ ሥራ ነዉ። በእርግጥ ሥራዉን እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሰይጣን ሊያግድህ ይሞክራል። ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል። በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል የሐሜት ጎርፍ ያስወርድብሃል። ደራሲያን ኦንዲጠይቁህ እጅግ ስመ ጥሩ ሰዎችም በክፋ እንዲናገሩብህ ይጠቀምባቸዋል። ጲላጦስ፥ሄሮድስ፥ሀናንያ፥ቀያፋ ሁሉም በአንተ ላይ ያድማሉ . . . አንተ ግን በፀና ውሳኔ በማያወላውል ቅናት በመጨረሻ ላደርገው የሰጠኽኝን ስራ ፈፀምኩ ሃይማኖቴንም ጠበቅሁ ለማለት እስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማ እና የተፈጠርክበትንም ግብ ተከተል።
አባ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፩፱፫፪፡፩፱፰፪ ዓ.ም.