New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የዐብይ ጾም ስብከት /ክፍል 6/

መጋቢት 20/2004 ዓ.ም.

በአያሌው ዘኢየሱስ

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

 

በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ውስጥ የምናነበው ወንጌል የሚያሳስበን ስለ በጎና ታማኝ አገልጋይ የተነገረውን ምሳሌ ነው፡፡ በዚህ የወንጌል ንባብ ውስጥ ጌታ በምሳሌ አድርጎ በመጨረሻው የፍርድ ቀን ሰዎች እንደ ሥራቸው እንደሚዳኙ በሰፊው አስተምሯል፡፡ በዚህ ምሳሌ ውስጥ አንድ ጌታ ለሦስት ባሮቹ ለእያንዳንዳቸው እንደ አቅማቸው ለአንዱ አምስት መክሊት፣ ለአንዱ ሁለት መክሊትና ለሌላው ደግሞ አንድ መክሊት ከሰጣቸው በኋላ ነግዱና አትርፉ በማለት እርሱ ወደ ሌላ አገር መሄዱ ተገልጦአል፡፡ በዚህም መሠረት አምስት መክሊት የተቀበለው የመጀመሪያው ባሪያ በተሰጠው አምስት መክሊት ቆላ ወርዶ ደጋ ወጥቶ ከነገደ በኋላ አምስት ተጨማሪ መክሊቶችን በማትረፍ አኖረ፡፡ ሁለት መክሊቶችን የተቀበለው ሁለተኛው ባሪያም በተሰጡት አምስት መክሊቶች ከነገደ በኋላ ሌሎች ተጨማሪ ሁለት መክሊቶችን አትርፎ አስቀመጠ፡፡ ሦስተኛው ባሪያ ግን ከእነዚህ ሁለት ባሪያዎች በተለየ ሳይወጣና ሳይወርድ፣ ሳይደክምና ሳያተርፍ በአቅሙ መጠን በተሰጠው አንድ መክሊት ሥራ ሳይሠራ እንዲሁ ወስዶ ጉድጓድ በመቆፈር ቀበረው፡፡