New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የጎንደር ከተማ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ

ግንቦት 25ቀን 2007 ዓ.ም

ዲ/ን ዘአማኑኤል አንተነህ ከጎንደር ማእከል

ከግንቦት 22-23 ቀን 2007 ዓ.ም በመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና በደብረ ጽጌ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንት ቤተክርስቲያን 3ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ሲካሄድ በጉባኤው ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤት ምክትል ኃላፊ መልአከ በረሃ ገብረ ሥላሴ አድማሱ ናቸው፡፡ በአንድነት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው በአፈጻጸማቸው ከ1-3 ለወጡት ለደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዳሴ ለገብርኤል ሰንበት ት/ቤት፤ ለልደታ ለማርያም ሰንበት ት/ቤትና ለወልደነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ሰንበት ት/ቤት በቅደም ተከተል ተሸልመዋል፡፡ ልምዳቸውንም አካፍለዋል፡፡ በሰንበት ት/ቤቶች በአገልግሎት ዘመን ቆይታ ያላቸው ወንድሞች የሕይወት ልምዳቸውንና ምክራቸውን ለጉባኤው ተሳታፊዎች አካፍለዋል፡፡