‹‹ታጠቡ ንጹሐንም ሁኑ›› /ት.ኢሳ. ፩፡፲፮/
ቤተ ክርስቲያን የግል ንጽሕናንና የአካባቢ ንጽሕናንም መጠበቅ እንደሚገባ የጤና ሥርዓት ሳይዘረጋ በቀድሚነት አስተምራለች፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ‹‹ታጠቡ ንጹሐንም ሁኑ፤ የሰውነታችሁን ክፋት ከዐይኖቼ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግንም ተው፤ መልካም መሥራትንም ተማሩ›› /ት.ኢሳ. ፩፡፲፮/ እንዲል የሥጋንም የነፍስንም ንጽሕና መጠበቅ ክርስቲያናዊ መመሪያ ነው፡፡