የሆሣዕና ምንባብ7(ማር. 10፥46-ፍጻ.)

 ወደ ኢያሪኮም ገባ፤ ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር ነበሩ፤ ብዙ ሰውም ነበረ፤ የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጤሜዎስም በመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር፡፡ የናዝሬቱ ኢየሱስ እንደ ሆነም ሰምቶ፥ “የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ” ብሎ ጮኸ፡፡ ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን ድምፁን ከፍ አደረገና፥ “የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ” አለ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ቆመና፥ “ጥሩት” አለ እነርሱም ዕውሩን ጠሩት፤ “በርታና ተነሥ፥ መምህር ይጠራሀል” አሉት፡፡ እርሱም ተነሥቶ ልብሱን ትቶ ወደ ጌታችን ኢየሱስ መጣ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥ “ምን ላደርግልህ ትሻለህ?” አለው፤ ዕውሩም፥ “መምህር ሆይ፥ እንዳይ ነው” አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም፥ “ሂድ፤ እምነትህ አዳነችህ” አለው፤ ወዲያውም አየ፤ በመንገድም ተከተለው፡፡

የሆሣዕና ምንባብ6(ማቴ. 20፥29-ፍጻ.

ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ ብዙ ሰዎች ተከተሉት፡፡ እነሆ÷ ሁለት ዕውራን በመንገድ አጠገብ ተቀምጠው ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስም ሲያልፍ ሰምተው፥ “አቤቱ፥ የዳዊት ልጅ፥ ይቅር በለን” እያሉ ጮኹ፡፡ ሕዝቡ ግን ዝም እንዲሉ ይቈጡአቸው ነበር፤ እነርሱ ግን፥ “አቤቱ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረን” እያሉ አብዝተው ጮኹ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ቆሞ ጠራቸውና፥ “ምን ላደርግላችሁ ትወዳላችሁ?” አላቸው፡፡ እነርሱም፥ “አቤቱ፥ ዐይኖቻችን እንዲከፈቱ ነው” አሉት፡፡ ጌታችን ኢየሱስም አዘነላቸው፤ ዐይኖቻቸውንም ዳሰሳቸው፤ ወዲያውም አዩና ተከተሉት፡፡

የሆሣዕና ምንባብ5(ሉቃ.19÷1-11)

ጌታችን ኢየስስም ወደ ኢያራኮ ገብቶ በዚያ ያልፍ ነበር፡፡ እነሆ÷ የቀራጮች አለቃ ስሙ ዘኬዎስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም ባለጸጋ ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስንም ያየው ዘንድ÷ ማን እንደ ሆነም ያውቅ ዘንድ ይሻ ነበር፤ የሰው ብዛትም ይከለክለው ነበር፤ ቁመቱ አጭር ነበርና፡፡ ወደ ፊቱም ሮጠ፤ ያየው ዘንድም በሾላ ላይ ወጣ፤ በዚያች መንገድ ያልፍ ዘንድ አለውና፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ወደዚያ በደረሰ ጊዜ አሻቅቦ አየውና÷ “ዘኬዎስ ሆይ÷ ፈጥነህ ውረድ፤ ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ አለኝና” አለው፡፡ ፈጥኖም ወረደ፤ ደስ እያለውም ወደ ቤቱ ይዞት ገባ፡፡ ሁሉም አይተው “ወደ ኀጢኣተኛ ሰው ቤት ሊውል ገባ” ብለው አንጐራጐሩ፡፡ ዘኬዎስም ቆመና ጌታችንን እንዲህ አለው÷ “ጌታዬ ሆይ÷ አሁን የገንዘቤን እኩሌታ ለነዳያን እሰጣለሁ፤ የበደልሁትም ቢኖር ስለ አንድ ፋንታ አራት እጥፍ እከፍለዋለሁ፡፡” ጌታችን ኢየሱሱም እንዲህ አለው÷ “ዛሬ ለዚህ ቤት ሕይወት ሆነ፤ እርሱ የአብርሃም ልጅ ነውና፡፡ የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአልና፡፡” ይህንም ሲሰሙ፤ ምሳሌ መስሎ ነገራቸው፤ ወደ ኢየሩሳሌም ቀርቦ ነበርና፤ እነርሱም የእግዚአብሔር መንግሥት ወዲያውኑ የምትገለጥ መስሎአቸው ነበርና፡፡

 

ሆሣዕና (የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት)

የሆሣዕና ዋዜማ /የቅዳሜ ማታ/ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ።

ትርጉም“የፋሲካ በዓል ሳምንት ሲቀረው የእውነተኛ አምላክ ደቀ መዛሙርት የእግዚአብሔር ሀገር ወደ ሆነችው ደብረ ዘይት ቁልቁለት ሲደርሱ ወደ እርሱ ለመታዘዝ ቀረቡ፤ ብዙ ሕዝብ፣ ልጆችና ሽማግሌዎችም የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ተጭኖ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸው ዘንድ በፍጹም ደስታ ኢየሩሳሌም ገባ” ማለት ነው።

 
መልዕክታት
ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን። (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ኛ ጴጥ.1÷13 ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና ነቅታችሁ ኑሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስም ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡  (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
የሐዋ.8÷26-ፍጻ. የእግዚአብሔር መልአክም ፊልጶስን ተናገረው፤ እንዲህም አለው÷ “በቀትር ጊዜ ተነሣና በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ፡፡” ተነሥቶም ሄደ፡፡  (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

መዝ.80÷3 “ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ፡፡”

 

ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷

ወንጌል
ዮሐ.12÷1-11 ፋሲካ ከሚውልበት ከስድስተኛው ቀን አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
የሌሊተ ሆሣዕና መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወ።

ትርጉም፦“።

 
 
ምስባክ
 

መዝ.117÷26 “ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር ባረክናክሙ እምቤተ እግዚእብሔር፡፡ እግዚእብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ፡፡”

 

ትርጉም፦ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠልን፤

ወንጌል
ሉቃ.19÷1-11 ጌታችን ኢየስስም ወደ ኢያራኮ ገብቶ በዚያ ያልፍ ነበር፡፡ እነሆ÷ የቀራጮች አለቃ ስሙ ዘኬዎስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ዘነግህ/በጊዜ ዑደት ውስተ ቤተ መቅደስ።/መዝሙር(ከጾመ ድጓ)
ወ።

ትርጉም፦“።

 
 
ምስባክ
 

መዝ.121፥1 “ተፈሣሕኩ እስመ ይቤሉኒ ቤተ እግዚእ ብሔር ነሐውር። ወቆማ እገሪነ ውስተ አዕፃድኪ ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌምሰ ሕንፅት ከመ ሀገር።”

 

ትርጉም፦ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ስላሉኝ ደስ አለኝ፡፡ ኢየሩሳሌም ሆይ÷ እግሮቻችን በአደባባዮችሽ ቆሙ፡፡ ኢየሩሳሌምስ እንደ ከተማ የታነጸች ናት፡፡

ወንጌል
ማቴ. 20፥29-ፍጻ. ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ ብዙ ሰዎች ተከተሉት፡፡ እነሆ÷ ሁለት ዕውራን በመንገድ አጠገብ ተቀምጠው ነበር፤ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ምስባክ
መዝ.147÷1 ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር፡፡ ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን እስመ አጽንዐ መናስግተ ኆኃትኪ፡፡
 

ትርጉም:- ኢየሩሳሌም ሆይ÷ እግዚአብሔርን አመስግኚ÷ ጽዮንም ሆይ÷ አምላክሽን አመስግኚ፤ የደጆችሽን መወርወሪያ አጸንቶአልና÷ ልጆችሽንም በውስጥሽ ባርኮአልና፡፡
 
ወንጌል
ማር. 10፥46-ፍጻ. ወደ ኢያሪኮም ገባ፤ ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር ነበሩ፤ ብዙ ሰውም ነበረ፤ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ምስባክ
መዝ.117፥27 ግበሩ በዓለ በትፍሥሕት በኃበ እለ ያስተሐምምዎ
 
ትርጉም፦ ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠልን፤ እስከ መሠዊያው ቀንዶች ድረስ በሚያስተነትኑበት በደስታ በዓልን አድርጉ፡፡
ወንጌል
ሉቃ. 18፥35-ፍጻ. (ተጨማሪ ያንብቡ)
ምስባክ
መዝ. 67፥34
 
ትርጉም፦
ወንጌል
ማቴ. 9፥26-ፍጻ. (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
መዝሙር ዘምዕዋድ አርእዩነ ፍኖቶ
አርእዩኖ ፍኖቶ ወንሑር ቤቶ እስመ እምጽዮን ይወጽእ ሕገ ወቃለ እግዚአብሔር እምኢየሩሳሌም ንሣለማ ለመድኃኒትነ በትፍሥሕት ተቀበልዋ ለታቦት እስመ ዋካ ይእቲ ወብርሃን

ትርጉም“።

 
መዝሙር ሰመያ አብርሃም
ሰመያ አብርሃም ወይቤላ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ በዕምርት ዕለት በዓልነ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን

ትርጉም“።

 
መዝሙር ወትቤ ጽዮን
ወትቤ ጽዮን አርኅው ሊተ አናቅጸ ይባኡ ሕዝብ ብዝዙኃን ወያዕትቱ ዕብነ እምፍኖት ለንጉሥ  ለወልደ ዳዊት ንጉሦሙ ለእስራኤል ውእቱ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም

ትርጉም“።

 

መዝሙር ባርኮ ያዕቆብ

ባረኮ ያ ዕቆብ ለይሁዳ ወልዱ ወይቤሎ ሀሎ ንጉሥ ዘይወጽ እ እምኔከ ዘየሐጽብ በወይን ልብሶ ወበደመ አስካል ሰንዱኖ ንጉሦሙ ውእቱ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም

ትርጉም“።

 
መልዕክታት
ዕብ. 9÷11-ፍጻ. ክርስቶስ ግን ለምትመጣይቱ መልካም ነገር ሊቀ ካህናት ሆኖ÷ የሰው እጅ ወደ አልሠራት÷ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ኛጴጥ.4÷1-12 ክርስቶስ ስለ እኛ በሥጋው ከተሰለቀ÷ እናንተም ይህቺን ዐሳብ ጋሻ አድርጋችሁ ኑሩ፤ በሥጋዉ መከራ የተቀበለ ከኀጢአት ድኖአልና፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
ሐዋ.28÷11-ፍጻ. ከሦስት ወር በኋላም በዚያች ደሴት ወደ ከረመችው ወደ እስክንድርያ መርከብ ወጣን፤ በዚያች መርብ ላይም የዲዮስቆሮስ ምልክት ነበረባት፤ ይኸውም “የመርከበኞች አምላክ” የሚሉት ነው፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

መዝ.8÷2 “እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡”

 

ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ወንጌል
ዮሐ.5÷11-31 እርሱም መልሶ÷ “ያዳነኝ እርሱ፡- አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ” አላቸው፡፡ አይሁድም÷ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ቅዳሴ
Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE MicrosoftInternetExplorer4 Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE

ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ

መዝሙሩንና ምንባባቱን በዜማ ለማዳመጥ ይህን ይጫኑ