የተራራው ምስጢር/ማቴ 17፡1-9/
ዲያቆን ታደለ ፈንታው
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊልጶስ ቂሣርያ መነ ይብልዎ ሰብእ ለወልደ እጓለ እመሕያው የሰው ልጅን ማን እንደሆነ ይሉታል ? የሚል ጥያቄን ለደቀ መዛሙርቱ አቀረበላቸው ፡፡ አንዳንዶች ከነቢያት አንዱ ነህ አሉት ፡፡ በሥምም እየጠቀሱ መጥምቁ ዮሐንስ : ኤልያስ : ኤርምያስ ነህ በማለት ግምታቸውን አስቀመጡ፡፡ ደቀመዛሙርቱ በቅዱስ መጽሐፍ እንደተነገረ ገና በእምነት አልጠነከሩም ነበርና ግምታቸው የተዘበራረቀ ነበረ፡፡