«ሙሽራ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው»
ከመስከረም 26 እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው ጊዜ ዘመነ ጽጌ ይባላል፡፡ በዚህ ዘመን ውስጥ አምስት ወይም ስድስት እሑዶች ይውላሉ፡፡
በእነዚህ እሑዶች በቤተክርስቲያን የሚሰጡትን ትምህርቶች አቅርበናል፡፡
የመጀመሪያ እሑድ
ዮሐ. 3-29
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ በልደቱ ጌታን በ6 ወር እንደሚቀድመው ሁሉ በይሁዳ አካባቢዎች እየተዘዋወረ «መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ» አያለ ማስተማር የጀመረውም ጌታችን ማስተማር ከመጀመሩ 6 ወር ያህል ቀድሞ ነው፡፡