አመልካች /Demonstratives/

 ነሐሴ 8 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

1. መራሕያን ያልናቸው ሁሉ አመልካቾች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የሚታወቁት ግን እንደሚከተለው በምሳሌ ቀርበዋል፤

ተክለ ማርያም ሖረ ኀበ ደብረ መንክራት

ውእቱ ሖረ ኀበ ደብረ ሊባኖስ

ውእቱ ብእሲ ሖረ ኀበ ደማስቆ

ይእቲ ወለት በልዐት ኅብስተ

ውእቶሙ ሙሉድ አእመሩ ትርጓሜ መጻሕፍት

ውእቶን አንስት ሰገዳ ለእግዚአብሔር አምላከ ኢትዮጵያ

ውእቶን አዋልድ በልዓ ኅብስተ

እሙንቱ ውሉድ አንበቡ ወንጌለ ዮሐንስ

እማንቱ አንስት ሰገዳ ለእግዚአብሔር አምላከ ኢትዮጵያ

ነጠላ                         ብዙ
ውእቱ ያ (that)          ውእቶሙ (ሙንቱ) እነዚያ (those)

ይእቲ ያቺ                  ውእቶን (ማንቱ)

  • እነዚህ ሁሉ የሩቅ ወይም በኅሊና ያለን ነገር ያመለክታሉ፡፡

2. ዝንቲ ብእሲ ሖረ ኀበ ኢየሩሳሌም፣ ይህ ሰው ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ፡፡

ዝ ብእሲ ሖረ ኀበ ኢየሩሳሌም፣
ዛቲ ብእሲት መጽአት እምደብረ ታቦር፣ የቺ ሴትዮ ከደብረ ታቦር መጣች፡፡
ዛቲ ብእሲት መጽአት እምደብረ ታቦር፣
እሉ ሰብዕ ሖሩ ኀበ ደብረ ከርቤ ግሸን፣ እነዚህ ሰዎች ወደ ደብረ ከርቤ ሔዱ
እላ ደናግል ቅዱሳት እማንቱ፣ እነዚህ ደናግል ቅዱሳት ናቸው

ነጠላ                            ብዙ
ዝ፣ ዝንቱ ይህ (This)        እሉ እነዚህ (These)

ዛ፣ ዛቲ ይች                   እላ እነዚህ

  • እነዚህ ሁሉ የቅርብን ነገር ያመለክታሉ፡፡

3. ዝኩ መምህረ ቅኔ ውእቱ = ያ ሰው የቅኔ መምህር ነው፡፡

እንትኩ ወለት እኀተ ሙሴ ይእቲ ያቺ ልጅ የሙሴ እኅት ናት

እንታክቲ አስካለ ማርያም ይእቲ

እልኩ ሰብእ ኢትዮጵያዊያን ውእቶሙ = እነዚያ ሰዎች ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡

እልክቱ

እልክቶን ደናግል መጽኣ እምገዳም = እነዚያ ደናግል ከገዳም መጡ፡፡

ነጠላ                                           ብዙ

ዝኩ፣ ዝክቱ (ዝለኩ) = ያ (that)        እልኩ፣ እልክቱ = እነዚያ (those)

እንትኩ፣ እንታክቲ = ያቺ                  እልኮን፣ እልክቶን = እነዚያ

  • እነዚህ ደግሞ እንደ ተራ ቁጥር አንድ የሩቅ ነገርን ያመለክታሉ፡፡

መልመጃ

አዛምድ (አስተፃምር፣ አስተዛምድ)

  1.  ዝኩ           አ. ሖረት

  2. ውእቱ          በ.ቀደስኪ

  3. አንታክቲ        ረ. መጽኣ

  4. እልክቱ         ደ. ነበሩ

  5. ይእቲ          ሀ. ሰገድኪ

  6. እሉ            ለ. ሖርነ

  7. እላ            ሐ. አንበብክሙ

  8. ዝክቱ          መ. ቀደሰ

  9. ዝንቱ          ሠ. ሐርክን

  10. እልኮን

  11. እልኩ

  12. እሙንቱ

የሚከተሉትን ወደ ግእዝ ተርጉም፤ ፈክር (ተርጉም) ኀበ ልሳነ ግእዝ

  1. ያች ልጅ ቆንጆ ናት፡፡

  2. እነዚያ ኤልሳቤጥና ማርያም ናቸው፡፡

  3. ያ የወንጌል ተማሪ ነው፡፡

  4. ይህ መጽሐፍ አዲስ ነው፡፡

  5. እነዚህ የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸው፡፡

              ሰላምታ

እፎ ኀደርከ ኁየ = እግዚአብሔር ይሰባሕ

(እንዴት አደርክ ወንድሜ) = (እግዚአብሔር ይመስገን)

ትምህርት እፎ ውእቱ = ሠናይ ውእቱ

(ትምህርት እንዴት ነው) = (ጥሩ ነው)

ማእዜ ውእቱ ዘፈጸምክሙ ፈተናክሙ = ዘዮም ወርኅ

(መቼ ነው ፈተናችሁን የጨረሳችሁት) = (የዛሬ ወር)

በጽባሕ አይቴ ሐዊረከ ውእቱ ዘኢረክብኩከ =ኀበ ከኒሣ /ቤተክርስቲያን/

(በማለዳው ያላገኘሁህ የት ሄደህ ነው) =ወደ ቤተክርስቲያን

በየነ ምንት =በይነ ነገረ ማርያም

(ስለምን) = (ስለ ነገረ ማርያም)

ኩሉ ሰብአ ቤትከ፣ እምከ፣ አቡከ፣ አኁከ፣ ደኅና ወእቶሙ = ወሎቱ ስብሐት

(ሁሉም ቤተሰቦችህ ደህና ናቸው) = (አዎ ምስጋና ለሱ ይሁን)

በል ሠናይ ምሴት ጌሰም ንትራከብ = ኦሆ ለኩልነ

( በል መልካም ምሽት ነገ እንገናኝ) = (እሺ ለሁላችን)