pop twadros election

የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 118ኛውን ፓትርያርክ መረጠች

ጥቅምት 26 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለ40 ዓመታት ቤተ ክርስቲያኗን ሲመሩ የነበሩትንና በቅርቡ ያረፉትን ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊን ለመተካት 118ኛውን ፓትርያርክ እሑድ ጥቅምት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. በታላቅ ሥነ ሥርዓት መረጠች፡፡

pop twadros electionበካይሮ አባሲያ ቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል በተደረገው የእጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት በእጩነት ከቀረቡት 3ቱ አባቶች መካከል አንዱን በፓትርያርክነት ለመሾም ዓይኑን በጨርቅ የተሸፈነ ሕፃን እጣውን እንዲያወጣ በማድረግ ብፁዕ አቡነ ታዋድሮስ / ቴዎድሮስ/ የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው ተመርጠዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ታዋድሮስ በ1952 እ.ኤ.አ የተወለዱ ሲሆን በፋርማሲ ሳይንስ ከአሌክሳንደሪያ ዩኒቨርስቲ ተመርቀዋል፡፡ከ1997 pop twadrosእ.ኤ.አ ጀምሮ በጵጵስና ተሹመው የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ላይ ነበሩ፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ አምስት ጳጳሳትን ያቀፈ ልዑክ ወደ ግብጽ በመላክ በምርጫው ላይ ተሳትፈው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡