kidusuraeal.jpg

የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ወጣቶች መንፈሳዊ የአገልግሎት ማኅበር ዓመታዊ በዓሉን አከበረ፡፡

በኅሩይ ባየ
በአዲስ አበባ ሃገረ ሰkidusuraeal.jpgብከት በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል አጥቢያ ዐሥራኹለት ቀበሌዎች የሚኖሩ ወጣት የቤተ ክርስቲያን ልጆች የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ. ም በደብረ ፅጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን የሰንበቴ አዳራሽ መንፈሳዊ የአገልግሎት ማኅበራቸው የተመሠረተበትን አንደኛ ዓመት አከበሩ፡፡ 
ቁጥራቸው ከአንድ ሺሕ በላይ የሆኑት እነዚህ ወጣቶች በአንድ ዓመት ቆይታቸው በየወሩ በተለያዩ አዳራሾች እየተሰበሰቡ ኦርቶዶክሳዊ የሃይ ማኖት ትምህርት ሲማሩ መቆየታቸውን የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ተስፋዬ አዳነ ገልጧል፡፡
 
«የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀና በተደራጀ መልኩ፤ ትምህርተ ሃይማኖትን ለመማርና በመልካም ሥነ ምግባር ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል መዋቅርና አሠራሯን ጠብቆ በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ መሰባሰብ የበለጠ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመ ንበታል፡፡ ስለዚሀ በአጥቢያችን በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስ ቲያን እየተገኘን መሰብሰብ ጀምረናል፡፡» ሲል የገለጠው ወጣት ተስፋዬ አዳነ፤ ወጣቶቹ በየሳምንቱ በአቅራቢያቸው ቤተ ክርስቲያን እየተገኙ ስብከተ ወንጌል መርሐ ግብሮችን እንደሚከታተሉና በወር አንድ ጊዜ ደግሞ በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ጉባኤያቸውን በማካሔድ የመዝሙር ጥናት እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንደሚማሩ ተናግሯል፡፡

ማኅበሩ በ2002 ዓ. ም ተመሥርቶ አገልግሎቱን መስጠት ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በርካታ መንፈሳዊ ተግባ ራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ጥቂቶቹ በእስር ቤት ያሉ ወገኖቻችን በዓል ጥምቀትን አስበው እንዲውሉ የምሣ ግብዣ ማዘጋጀት፤ የቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ በዓላት ኦርቶዶክሳዊ ትውፊቶችን ሳይለቁ እንዲከበሩ የግንዛቤ ማስጨ በጪያ ትምህርት ማካሔድ፤ ወጣቶች በቤተ ክርስቲያን ሥርዐት መሠረት ታቦተ ሕጉን አጅበው የንግሥ በዓላትን እንዲያከብሩና የሚጠበቅባቸውን አገል ግሎት እንዲያበረክቱ በማድረግ ካከናወኗቸው ተግባራት ጥቂቶች እንደሆኑ በዕለቱ የቀረበው ሪፖርት ያስረዳል፡፡

ማኅበሩ በቀጣዩ የሥራ ጊዜ ካቀዳቸው ተግባራት ዋናዋናዎቹ፤ በቤተ ክርስቲያናችን የተቀጣጠለውን ውጫ ዊና ውስጣዊ ፈተና ለመቋቋም ዋናው መሣሪያ ጸሎት ስለሆነ በሳምንት አንድ ቀን የማኅበር ጸሎት ማድረስ፤ በተጀመረው የዐቢይ ጾም ወራት እያንዳንዱ የማኅበሩ አባል ቁርሱን ለነዳያን እንዲሰጥ ማድረግ፤ በምግብና በልብስ እጦት ምክንያት ከእናት ቤተ ክርስቲያናቸው ወደ ሌላ የእምነት ተቋም እንዳይፈልሱ አሳዳጊ አልባ የሆኑ ሕፃናትን እና ጧሪ ያጡ አረጋውያንን በግልና በቡድን መርዳት፤ በትምህርተ ሃይማኖት እውቀት ማነስ ምክንያት ወጣቶች በነጣቂ ተኩላ እንዳይወሰዱ ከአጥቢያቸው የሰበካ ጉባኤ እና ከሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዐት፣ ታሪክና ትውፊት ትምህርቶች እንዲከታተሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እና በቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ደጋግ አባቶችን በዓለ ልደታቸውን እና ዕረፍታቸውን ማክበር በሁለት ወር አንድ ጊዜ የሚታተም መንፈሳዊ መጽሔት ማዘጋጀት ዋና ዕቅዳቸው መሆኑን ወጣት ተስፋየ አዳነ ገልጧል፡፡

 
/ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ከመጋቢት 1-15 ቀን 2003 ዓ.ም/