የክብረ ገዳማት የቀጥታ ዘገባ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

እንደምን ዋላችሁ ውድ ምእመናን አሁን የክብረ ገዳማትን የቀጥታ ዘገባ ለማቅረብ እንሞክራለን።

9:23 በዝናብ ምክንያት ዘግየት ብሎ የጀመረው ይህ መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተደረገ ይገኛል።

አዳራሹ ሞልቶ ምእመኑ ቆሞ በሚታይበት ሁኔታ በዚህ አመት ሙሉ ፕሮፌሰርነት ያገኙት ፕርፕፌሰር ሽፈራው በቀለ የጥናት ጽሁፋቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

“የገዳማት ደጀሠላሞች ዋጋ እንደሌላቸው ታስቦ መፍረስ የለባቸውም። የገዳማት የትኛውም ቤት ከመፍረሱ በፊት በአርኪኦሎጂስቶች መታየት አለባቸው”

ፕሮፌሰር እንዳሉት በሀገራችን አንድ ባህል አለን በክፉ ቀን የከበረን ነገር መሬት ውንጥ መቅበር፣ ስለዚህ እንደተቀበረ ሊቀር ይችልሉና ገዳማትና አድባራት በጥ ንቃቄ ሊያዙ ይገባቸዋል።

በመካከለኛው ዘመን ገዳማከ የትምህርትና የባህል ማእከላት ነበሩ። በአክሱም ዘመነ መንግስት የጀመረው የገዳም ሥር ዓት በዛግዌ ጊዜ ወደ በጌምድር፣ ሸዋ፣ ወሎ አንዲሁም ወደ ደቡብ ክልሎች ተስፋፍትዋል።

9:40 ም እመናን  በተለያዩ ምክንያቶች መቆራረጡን ታግሳችሁ አሁንም ከእኛ ጋር እንደምትሆኑ እናስባለን

አሁንም ፕሮፌሰር ሽፈራው የጥናት ጽሁፋቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

ገዳማት በተለያዩ ዘመናት ከሚገጥማቸው ችግሮችን ለምሳሌ መውደማቸውን ግንዛቤ ውስጥ አስገብተን ጥልቅ የአርኪኦሎጅ ጥናት ያስፈልጋል።

ገዳማት የቅርስ የጥበብ ምንጮች ናቸው። መስቀል በተለያዩ መልኮች የሚሰራበት ቤተ ክርስቲያን በየትም የለም፤ በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያንት ዘንድ ቢሆን።

9:55 አሁን ማኅበረ ቅዱሳን በገዳማት በኩል ያደረገውን የ10 ዓመት የልማት እንቅስቃሴ አስመልክቶ ሪፖርት በወ/ሮ አለም ጸሐይ መሠረት እየቀረበ ነው።

“የግራኝ ዜና መዋ ዕል ጸሐፊ ከየረር እስከ አዋሽ ወንዝ ድረስ ብዙ ገዳማት መቃጠላቸውን ገልጽዋል።” ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ

“በቀደምት የኢትዮጵያ ታሪክ የመንግስታት መጠናከር ለገዳማትና አድባራት መጠናከር አስተዋጾ ነበርው” ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ

“ከአፄ ቴዎድሮስ ጀምሮ እየተጠናከረ የመጣው የገዳማት ሁኔታ በደርግ ዘመነ መንግስት ተዳፈነ።” ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ

9:57 “በቆላ ተምቤን ከሚገኙት ወደ 28 የሚጠጉ ገዳማት አንዱ አብራ አንሳ ነው፤ አፄ ግ/መስቀል የመነኮሳቱን ብዛት አይተው እንደ አሳ ይበዛሉ ለማለት ስሙን እንደሰጡት ይነገራል። ዛሬ ግን 5 መነኮሳት ብቻ ቀርተዋል።” ወ/ሮ ዓለምፀሐይ

“እኛ ወደ ቦታው በሄድንበት ወቅት የሚበላ ስላልነበራቸው ከሳምንት በፊት የመጣ ጠላ ብቻ ሊሰጡን ችለዋል።”

“ሌላ ጊዜ አባ ሳሙኤል ወደ ሚባል ገዳም ሄድን፤ መቅደሱ ፈርስዋል፣ የመነኮሳትም መኖሪያ ፈርሶ ደግር ሆንዋል። አሁን በካህን ይለገላል”

“የአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃንን ገዳምን 4 ብቻ መነኮሳት የሚመግበው የ16 ዓመት ልጅ ነበር” ምእመናን ከላይ የቀረቡት ከወ/ሮ ዓለም ፀ ሐይ የግል የውሎ ዘገባ የቀረቡትን እጅግ ጥቂት ችግሮችን ነው። ከዚህ የከፋ ችግር ያለባቸው እንዳሉ ለመግለጽ እንወዳለን።

ለእነዚህ ገዳማት የቤተ ክርስቲያናችን የልማት ኮሚሽን የሚሰራው ሥራ ቢኖርም ማኅበረ ቅዱሳን ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው መመሪያ መሠረት መሥራቱ የግድ ሆኖበታል። ብለዋል ወ/ሮ ዓለምፀሐይ

ስለሆነም ማኅበሩ ገዳማቱ ያላቸውን ሃብት በመጠቀም ዘላቂ ፕሮጀክክት ይሠራል። በዚህም ገዳማቱ ከቁሪትነት እንዲወጡ እንዲሁም እንዳይፈቱ ያደርጋል።

10:19 አቶ አጥናፍ ከ1992-2002 ዓም በማኅበሩ የተሰሩ ሥራዎችን ዳሰሳ አቅርበዋል።

ፕሮጀክቶቹ ከአነስተኛ ጊዜአዊ ድጋፍ እያደጉ የሄኡ ናቸው። ከ2000 ብር ሥራ የጀመረው የፕሮጀክት ሥራ አሁን እስከ 5 ሚሊዮን ብር የሚደርሱ የፕሮጀክት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

እስከ አሁን በ6.9 ሚሊዮን ወደ 73 የሚጠጉ ፕሮጀክቶች ተተግብረዋል።

10:30 ክብረ ገዳማት ዘጋቢ ፊልም እየቀረበ ነው።

እስከ አሁን በተሰሩት ሥራዎች ገዳማቱ በራሳቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ የተረዱበት ነው።

የዘጋቢ ፊልሙ ርዕስ “ሥርዓተ ገዳም በኢትዮጵያ”  ይሰኛል።

10:55 በቀጣይ ዓመታት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንደ አብረንታንት ዋልድባ፣ ደብረ በንኮል ባሉ ገዳማት ለመሥራት አቅደናል።

“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ተቀምጠውበታል ወደ የሚባለው ጉንዳጉንዲ ስንሄድ የተቀበሉን አንድ መነኮስ ብቻ ነበሩ።” ዲ/ን ደረጀ ግርማ

ለ2004 ዓ.ም ወደ 18 የሚጠጉ ፕሮጀክቶች ለገዳማት አቅደናል። እነዚህ ፕሮጀክቶች ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ ችግር እጅግ የጸናባቸው ናቸው። ዲ/ን ደረጀ የቃል መግቢያ ሰነዱን እያአስተዋወቁ ይገኛሉ።

“አብረን እንሥራ ለውጥ እናመጣለን” በማለት ዲ/ን ደረጀ መልእክት አስተላልፈዋል።

ለገዳማት እርዳታ ለማድረግ የምትፈልጉ gedamat_mk@yahoo.com ወይም 0173036604664000 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አራት ኪሎ ቅርንጫፍ

11:10 አሁን የምእመናን አስተያየት እየተደመጠ ነው።

“ታሪክ እየጠፋ ኢትዮጵያዊነት የለም። ገዳማት ደግሞ የታሪክ ምንጮች ናቸውና የቻልነውን ልናደርግ ይገባል።”

“ይህን መርሐ ግብር በሌሎች አድባራትም ብታደርጉት የተሻለ ገንዘብ በመሰብሰብ ገዳማትን መርዳት ይቻላል።”

“እናንተ እንደተለመደው አስታውሱን እንጅ ከአሰብነው በላይ እንሰጣለን።”

“ሌሎች የጠፉ ገዳማትንም ብታስታውሱን”

“ሦስት አራት ሆነን መርዳት እንችላለን?” “ይችላል፣ ለደረሰኝ እንዲመች ግን በአንድ ስም ብትከፍሉ ይሻላል።”

ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

አባታችን ሆይ