የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (ሦስተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
 
‹‹ ጌታ ማኅየዊ ›› የተባሉት ቃላት ለአምላክ ብቻ የሚሰጡ ናቸው፡፡ ስለዚህም መንፈስ ቅዱስ ‹‹ ጌታ ማኅየዊ ›› መሆኑንና አምላክነቱንም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃል በማረጋገጥ ፣ የመንፈስ ቅዱስ ተቃዋሚዎችን የረቱት የጥንቶቹ የቤተ ክርስቲያን አባቶች በአንቀጸ ሃይማኖታቸው ደንግገውልናል፡፡ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ጋር እኩል ስለሆነ ከእነርሱ ጋር ልንሰግድለትና ልናመሰግነው እነደሚገባን አስተምረውናል፡፡