ትንሣኤ ግዕዝ

 

/ርት ፀደቀ ወርቅ አስራት

የጥንቱ ውበቱ

ጭራሽ ተዘንግቶ፣

ለብዙ ዘመናት

የሚያስታውስ አጥቶ፣

ተዳክሞ ቢያገኙት

ግዕዝ አንቀላፍቶ፣ 

«ሞተ ሞተ» ብለው

አዋጅ አስነገሩ፣

በርቀት እያዩ

ቀርበው ሳያጣሩ፡፡

ታዲያ ይሄን ጊዜ…..

አዋጁን የሰሙት

ቀርበው ወገኖቹ፣

ፍፁም እያነቡ

ግዕዝ….. ግዕዝ ቢሉ

አብዝተው ቢጣሩ፣

በቅፅበት ተነሣ፣

ትንሣኤን አግኝቶ

ለወዳጆቹ ጥሪ

ምላሽ ሊሰጥ ሽቶ፡፡