atens 01

በግሪክ አቴንስ ዐውደ ርእይ ተካሔደ

ነሐሴ 19 ቀን 2006 ዓ.ም.

አውሮፓ ማእከል

atens 01በግሪክ አቴንስ ምክሓ ደናግል ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤና ሰንበት ትምህርት ቤት ከማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል ጋር በመተባበር ከነሐሴ 9 እስከ 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ዐውደ ርእይ ተካሔደ፡፡

ለተከታታይ ሦስት ቀናት የቆየው ዐውደ ርእይ በበርካት ምእመናን የተጎበኘ ሲሆን፤ የቤተ ክርስቲያን ጥንታዊ ታሪክ፣ የገዳማትና አብነት ትምህርት ቤቶች ወቅታዊ ሁኔታ፣ የማኅበረ ቅዱሳን አመሠራረትና መንፈሳዊ አገልግሎት በተመለከተ ገለጻ ተደርጓል፡፡ ዐውደ ርእዩን የተመለከቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ምእመናንም አስተያየታቸውን በቃልና በጽሑፍ ሰጥተዋል፡፡

atens 04በተለይም ገዳማትና አብነት ትምህርት ቤቶች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ ከቀረበው ገለጻ መረዳታቸውንና ማዘናቸውን የገለጹት ምእመናን፤ በገዳማትና በአብነት ትምህርት ቤቶች ላይ የሚታየው ችግር ለመፍታት ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር በመሆን አቅማቸው የፈቀደውን ድጋፍ ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

በዚህም መሠረት ማኅበረ ቅዱሳን አብነት ትምህርት ቤቶችን ለመርዳት የቀረጸውን የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የነጻ ትምህርት እድል ፕሮጀክት ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ፕሮጀክቱም በተያዘለት እቅድ መሠት እስኪፈጸም ድረስ ድጋፋቸውን አጠናክረው ለመቀጠል ቃል ገብተዋል፡፡

በተጨማሪም ገዳማትንና አብነት ትምህርት ቤቶችን በጋሪ ለመርዳት እንዲያስችል ማኅበረ ቅዱሳን በግሪክ አቴንስ ከተማ ማእከል እንዲያቋቁምላቸው ምእመናን ጥያቄ አቅርበዋል፡፡atens 03

ማኅበረ ቅዱሳን በቅርቡ በጀርመን ካስል ደብረ ቀራንዮ መድኃኔዓለም እና በኮሎኝ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ዐውደ ርእይ አዘጋጅቶ እንደነበር መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን፤ ዐውደ ርእዩ በቤልጂየም ብራስልስ አብያተ ክርስቲያናትም ይቀጥላል፡፡