hall.jpg

በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና በመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የእግር ጉዞ ተዘጋጀ።

በኪ/ማርያም ወ/ኪሮስ
 
hall.jpg የደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ እያሰራ ላለው የሰንበት ት/ቤት እና የስብከተ ወንጌል ሁለገብ አዳራሽ ታህሳስ 10 ቀን 2003ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ መነሻው መስቀል አደባባይ መድረሻው በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን  የሚፈጸም  የእግር ጉዞ አዘጋጅተዋል።
  
 በዕለቱም ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት፣ታላላቅ የቤተክርስቲያን አባቶች፣ መምህራንና ዘማርያን፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ጋዜጠኞች፣ አርቲስቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ።

                    
“እርሶዎም እንዳያመልጦዎት አሁኑኑ ቲሸርቱን በ35 ብር በመግዛት ይጓዙ።” በማለት ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

poster.jpg

“ህንፃው ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክ ነው፤ ለሰው አይደለምና ሥራው ታላቅ ነው።”
                                                                    1ኛዜና መዋ 29፡1
ቲሸርቱ በደብሩ ንዋየ ቅዱሳት መሸጫ እና በደብሩ ልማት ጽ/ቤት ያገኛሉ።
ለበለጠ መረጃ
–    011-1-55-62-87
–    0911-15-44-47
–    0911-00-24-99
–    0911-11-69-56 ብለው ይደውሉ