በባሌ ሀገረ ስብከት የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ

በእንዳለ  ደምስስ

በባሌ ሀገረ ስብከት ሮቤ ከተማና አካባቢው ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ጥር 15 ቀን 2011 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ላይ ለጊዜው ባልታወቀ መንስኤ መቃጠሉን መ/ር ያሬድ ገ/ማርያም የወረዳው ቤተ ክህነት ጸሐፊ ገለጹ፡፡

የቃጠሎው መንስኤና የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ የገለጹት መ/ር ያሬድ፤ ቤተ ክርስቲያኑ በቃጠሎው ምክንያት ሙሉ ለሙሉ መውደሙንና በአገልጋዮችና በአካባቢው ምእመናን ጥረት ታቦቱን ብቻ ማዳን መቻሉን ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል፡፡ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን፡፡