ለሑዳዱ አዝመራ ተዋሕዶ ስትጣራ የቀጥታ ዘገባ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ማኅበሩ ለሚያደርገው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ፣ ሰለ አንዲት ነብስ መዳን የሰማይ መላእትም ምን ያህን እንደሚደሰቱ እናስተውል። ሐዋርያትም ደማቸውን ያፈሰሱባት አጥንታቸውን የከሰከሱባት አገልግሎት እርስዋ ናትና።

ከአሁን በህዋላ ወር በገባ በሁለተኛው ሳምንት ዘወትር ረቡዕ ስለ ስብከተ ወንጌል የምንነጋገርበት መርሐ ግብር ይኖራል።

“ለወደፊቱ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቀው ከንቀሳቀሱ ማኅበራትና ሰ/ት/ቤቶች ጋር እንሠራለን ይህም ችግሮቻችንን ያቃልልሉናል ብለን እናስባለን” ቀሲስ ታደሰ ጌታሁን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል አስተባባሪ

የገንዘብ ችግር፣ የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ችግሮች አገልግሎታችን እንዳይሰፋ እያደረጉት ነው”

“ማኅበሩ በአንድ ጊዜ በአራቱም አቅጣጫ ሐዋርያዊ ጉዞ ማካሄድ ይችላል። ነገር ግን የሚከተሉት ችግሮች ፊቱ ላይ ተደቅነዋል።”

“እግዚአብሔር ማኅበሩን አንደምክንያት አድርጎ እየተጠቀመ ያለበት ጊዜ ነውና ይመስገን፤ ያልተያዙትን ለመያዝ ሰንሄድ አብሮ ያሉትን ቢያጸና። ማኅበሩ ታች ወርዶ ማኅበራትን የሚያሰለጥንበት ሁኔታ ቢፈጠር ብዙ ሥራ ይሠራል”

“ያየሁት ዶክመንታሪ ፊልም ይበቃኛል፣ አስተያየት መስጠት አልፈልግም፤ በየ 3 ወሩ 5000.00 ብር ለዚህ አገልግሎት እሰጣለሁ።” በወረቀት የተሰጠ አስተያየት

“ማኅበሩ አዲስ አበባም ላይ ትኩረት ቢያደርግ፣ ግራ ተጋብተናልና”

“በግቢ ጉባኤ ያለፍን ተመራቂዎችም ተምረን ዝም ማለት የለብንም፣ እኔ አሁን በራሴ አፍሬያለሁ። ተምሬ፣ ሥልጠና ወስጄም ተቀምጫለሁ ስለሆነም የራሳችን ድርሻ ልንወጣ ይገባል።”

“አዲስ አበባ ለሚኖሩ ካህናት ሥልጠና ተሰጥቶ፣ ወደ አገር ቤት/ገጠር/ ሲሄዱ፣ የሚሄዱበትን አካባቢ እንዲያስተምሩ ቢደረግ”

“ያየሁት ድንቅ ነገር ነው። ልጄ ነውና ወደዚህ ያመጣኝና መርቁልኝ አሁንም መርቁልኝ”

10:47 የምእመናን አስተያየት እየተሰጠ ነው።

4. ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የበዙባቸው ነገር ግን ለድብቁ የመናፍቃን ሴራ የተጋለጡን ሁኔታዎችና አካባቢዎች ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው።

3. ሥልጠናን

2. አምነው፣ ተጠምቀው ነገር ግን በመናፍቃንና ተሐድሶ ኑፋቄ የተጠቁትን

1. ምንም ስብከተ ወንጌል ያልተስፋፋባቸውና በመግባቢያቸው መማር የሚፈልጉትን

ዶክመንታሪ ፊልሙ ከስብከተ ወንጌል አንፃር አራት መሠረታዊ ነጥቦችን ተንተርሶ ይተነትናል።

በዚህም ማኅበሩ የተለያዩ ክፍሎች ከጎኑ እንዲሆኑ ይፈልጋል። ማኅበሩ ባለው የገንዘብ አቅም ይህ ሁሉ ዓለም አቀፋዊ አገልግሎት ሊሸፍን አይችልም።

ስለዚህ የቅድስት ዋነኛ አገልግሎት የሆነውን የስብከተ ወንጌል ለማስፋፋት ወቅቱ የሚጠይቀውን ማድረግ ያስፈልጋል።

እነዚህ የትምህርት ክፍል አገልግሎቶች ከወደፊት ምን መሠራት እንዳለበት ለማመልከት በራሱ በቂ ሊሆን አይችልም።

እንዲሁም ለ1 ሥልጠና እስከ 65000 ብር ያስወጣዋል።

ማኅበሩን እስከ አሁን ካለው ልምድ ለ1 ሐዋርያዊ ጉዞ እስከ 40000 ብር ያስወጣዋል።

በተመረጡ የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጥናዎችም ተሰጥተዋል።

10 ዙር የሰባክያን ሥልጠናዎች ተደርገዋል።

ማኅበሩ በአገር ውስጥ ያልተወሰነው የሐዋርያውዊ አገልግሎቱ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በምሥራቅ አፍሪካ ወዘተ ይቀጥላል።

በማኅበሩ የሚዘጋጅ አንድ ሐዋርያዊ ጉዞ ወደ አምስት የሚጠጉ ከተሞችን የሚያካልል ነው። አንድ ልኡክ ከ25 እስከ 30 የሚጠጉ መምህራንን፣ መዘምራንን፣ የቀረጻና የሚዲያ ባለሙያዎችን ያካትታል።

ከሐመር የሠለጠኑት ደግሞ የጎሳውን መሪና 3000 የሚሆኑ ምዕመናንን አስተምረው ለማጥመቅ ችለዋል።

ከኑዌር ከሰለጠኑት ውስጥ የተወሰኑት ክህነት ተቀብለው ወደ 700 የሚጠጉ ምዕመናንን አስተምረው ለማጥመቅ ችለዋል።

ምዕመናን ያላቸውን ይዘው እንዲቆዩ የሚያደርግ፣ የቤተ ክርስቲያናቸው ፍቅር እንዲጨምር ፣ ካህናትም በቁጭት እንዲያገለግሉ የሚያደርጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙራትን ያስተማሩና ያሳወቁ ነበሩ

ማኅበሩ 19 ዙር ሐዋርያዊ ጉዞ አድርግዋል።

ከክኦሮሚያ እየሚሰጠው ሥልጠና የደቡብ፣ የኦሮምያ፣ የሶማሌ፣ የበቤንሻንጉልና የጋምቤላ  ክልሎችን ያቀፈ ነው።

ስብከተ ወንጌል ካልተስፋፋባቸው አካባቢዎች ለመጡ ከ200 በላይ ሰልጣኞች ለማፍራት ተችልዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን  በክረምቱ የሰባክያን ሥልጠና 1306 ሠልጣኞችን በ1003000 ብር በጀት አፍርትዋል።

9:40 ለሑዳዱ አዝመራ ተዋሕዶ ስትጣራ የሚለው ዶክመንታሪ ፊልም ተቀንጭቦ እየታየ ነው።

9:38 “ያሰባሰበን ቸሩ ፈጣሪ ይክበር የሁሉ ጌታ፣

ሁሉ ነገር ከእርሱ የማይወጣ ይወደስ በእልልታ” የሚለው መዝሙር በጋራ እየተዘመረ ነው።

“እናንተ ኢትዮጵያዊያን ለእኛ አፍሪካዊን ደም ተጠያቂዎች ናችሁ፣ ለምዕራባዊያን አስተሳሰብ፣ ባህል፣ ሃይማኖት አሳልፋችሁ ሰጥታችሁናልና። ”  ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ በመርሐ ግብሩ ከተናገሩት ገጠመኛቸው የተናገሩት

9:29 የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ያዘጋጀውና የማኅበሩን የ19 ዓመት የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴ የሚያስቃኘው ዶክመንታሪ ፊልም ለመታየት በዝግጅት ላይ ነው።

-9፡00 ላይ የማኅበሩ ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።

9:26 ምዕመናን “ማርያም ሀዘነ ልቡና ታቀልል…ማርያም የልብን ሀዘን ታቀላለች” የሚለውን መዝሙር በጋራ እየዘመሩ ነው።

8:45 የማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን ወረብ አቅርበዋል።

“ሠላመከ እግዚኦ ሀበነ

ወኢትግድፈነ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔነ

ከመ ኪያከ ንሰብህ በኩሉ መዋዕል ሕይወትነ ኢያማስነ ተስፋነ

ለእለ ንሴፈወከ ወተዘከር ዘንተ ተግባረከ”

 

እንደምን ዋላችሁ ክቡራን ምዕመናን ለሑዳዱ አዝመራ ተዋሕዶ ስትጣራ በሚል መሪ ቃል በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የተዘጋጀውን መርሐ ግብር በቀጥታ ለማስተላለፍ እንሞክራለን።

ምንም እንክዋን መርሐ ግብሩ 8:30 ቢጀምርም፣ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ዘግይተን ለመጀመር ተገደናል።

መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ የስብሰባ ማዕከል ለማዘጋጀት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ባጋጠመን ከአቅም በላይ ችግር ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ በታቀደለት መሠረት እየተካሄደ ይገኛል።

እግዚአብሔር ይመስገን